የኢትዮጵያ አየርመንገድ ግሩፕ በዘንድሮው የበጀት አመት 9.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መሰብሰቡን በዛሬው እለት አስታውቋል።
የግሩፑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት ይህ ገቢ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ20 በመቶ ብልጫ አለው።
ስራ አስፈጻሚው አየርመንገዱ ገቢ በመሰብሰብና አራት አዳዲስ መዳረሻዎችን በመክፈት በአመቱ ስኬታማ የሚባል አፈጻጸም አስመዝግቧል ብለዋል።
እንደ ኢቢሲ ዘገባ የአየርመንገዱ አጠቃላይ አለምአቀፍ መዳረሻዎች አሁን ላይ 150 ደርሰዋል።
አየርመገዱ በመካከለኛው ምስራቅ የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ በተከሰተው በነዳጅ አቅርቦት እጥረት ቢፈተንም ከፍተኛ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አቶ መስፍን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አየርመንገድ ባሉት የአውሮፕላኖችና በአለምአቀፍ የበረራ መዳረሻዎች ቁጥር ከአፍሪካ ቀዳሚ ነው።












