አይናለም ደስታ በያመቱ በሚካሄደው የአምስተርዳም ማራቶን፥ የሴቶች ውድድር አሸናፊ ሆናለች።
ለማራቶን አዲስ የሆነችው አይናለም በ 2፡17፡37 ውድድሩን በመጨረስ፥ በአምስተርዳም የተለመደውን የኢትዮጵያውያን አሸናፊነት ታሪክ አስጠብቃለች። በውድድሩ 3ኛ ኪሎሜትር ላይ ወይም ከ1፡38፡07 ጀምሮ አራት አትሌቶች ብቻ ከፊት ሆነው ሲመሩ ነበር። አራቱም ሴት አትሌቶች ኢትዮጵያውያን ናቸው። አይናለም በአንደኛነት ስታሸንፍ፥ ከሗላዋ ብርቱካን ወልዴ፥ መቅደስ ሽመልስ እና ዋጋነሽ መካሻን አስከትላ አጠናቃለች። አይናለም ከተከታይዋ በአራት ደቂቃ ቀድማ ስትጨርስ ከቀድሞዋ የአምስተርዳም ማራቶን ሪከርድ ባለቤት ያለም-ዘርፍ የሗላ በ45 ሰከንድ ብቻ ዘግይታ ሪከርዱን ለጥቂት ሳትሰብር ቀርታለች።













