ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሆነው ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሰለባ የሆነው የአለም የምግብ ድርጅት ኢንጂነር ቤተሰቦች የ29 ሚሊዮን ዶላር ካሳ እንዲከፈላቸው የአሜሪካ ፍርድ ቤት ወሰነ።
አውሮፕላኑ ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ እያቀነ በነበረበት ወቅት ጥቂት እንደተጓዘ በመሾፍቱ አካባቢ የተከሰከሰው እአአ በ2019 ነበር።
አየርላንዳዊው የ 39 አመቱ ሚካኤል ርያን በኢቦላ ቀውስ ወቅት ጭምር በላይቤሪያና በኢትዮጵያ ሲሰራ ቆይቷል። በአደጋው 32 ኬንያዊውንና ዘጠኝ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የ 157 ሰዎች ህይወታቸው አሎፏል።
ቦይንግ አብዛኞቹን ጥያቄዎች ከተጎጂ ቤተሰቦች ጋር ባደረገው የግል ድርድር ስምምነት ላይ ደርሷል። እአአ በ2020 አንድ ኬንያዊ ቤተሰብ የ3 ሚሊዮን ዶላር ለመቀበል ሲስማማ፣ ራያን ግን ጉዳዩን ወደ አሜሪካ ፍርድ ቤት ወስዶ ሲከራከር ቆይቶ በመጨረሻም የፍርድ ውሳኔ ተሰጥቶለታል።
የአሜሪካ ፍርድ ቤት ባለፈው ግንቦት ወር ለአሜሪካዊው ሳሚያ ስቱሞ ቤተሰቦች የ49.5 ሚሊዮን ዶላር ካስ እንዲከፈላቸው ውሳኔ ማስተላለፉ የሚታወስ ነው።










