በኢቦላ የተጠቃው ይህ ግለሰብ በዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሰብዓዊ እርዳታ ሲሰጥ ቆይቶ የተመለሰ ዶክተር ነው ተብሏል።
ዶክተሩ ወዲያውኑ ወደ ልዩ ሆስፒታል መግባቱንና በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሮይተርስ የፈረንሳይ ጤና ሚኒስቴርን ጠቅሶ ዘግቧል።
ዲአርሲ የኢቦላ ወረርሽኙ የተከሰተው ባለፈው ወር እንደሆነ ብትገልጽም ባለሙያዎች ግን ቫይረሱ ከእዚያ በፊት ለሳምንት ያህል ሳይሰራጭ እንዳልቀረ ያምናሉ። በሀገሪቱ በቫይረሱ ከ260 በላይ ሰዎች የሞቱ ሲሆን ከ1000 በላይ ደግሞ በቫይረሱ መያዛቸው ተገልጿል።
ባለፈው ወር በዲአርሲ በቫይረሱ የተያዘ አሜሪካዊ ዶክተር በጀርመን ሆስፒታል የታከመ ቢሆንም ይህ ህመም(case) በአውሮፓ ውስጥ ሲመዘገብ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ቫይረሱ ወደ ጎረቤት ዩጋንዳ ተስፋፍቶ ቢያንስ 20 ሰዎችን ማጥቃቱን የአለም ጤና ድርጅት ማረጋገጡ ይታወሳል።











