አለምአቀፉ የነፍስ አድን ቡድን በቬንዙዌላ በተከሰተውና በማግኒቲዩድ 7.2 እና 7.5 በተለካው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ የተረፉ ሰዎች ለማውጣት ተቀላቅለዋል።
በሰሜንና ደቡብ አሜሪካ ያሉት ሀገራት ማለትም ሜክሲኮ፣ ብራዚል፣ካናዳ፣ ኩባና አሜሪካ እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የነፍስ አድን ሰራተኞችን ሰብአዊ እርዳታ ማቅረባቸውን ዛሬም ቀጥለውበታል። የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንዳሉት ከሆነ በአደጋው እስካሁን ህይወታቸው ያለፉት ሰዎች ቁጥር 920 ነው።
ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ በሀገሪቱ በምዕተ አመት ውስጥ ከተከሰቱት ሁሉ ከፍተኛ መጠን ያለውና ንዝረቱ በአጠቃላይ ቀጠናው መድረሱን አለምአቀፍ የመገናኛ ብዙኻኖች ዘግበዋል። በአደጋው ህይወታቸውን ካጡት በተጨማሪ ሌሎች 3000 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል።
የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር ካርሎስ አልቫራዶ እንደተናገሩት ሆስፒታሎች በቁስለኞች ተጨናንቀዋል።በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በፍስራሾች ስር ተዘግተው እንደማይቀሩ ተሰግቷል።
በዋና ከተማ ካራካስ በስተሰሜን የምትገኘው ላ ጓይራ የተባለች ግዛት በከፍተኛ ሁኔታ ከተመቱት ግዛቶች አንዷ ነች። በእዚች ግዛት ከ100 በላይ ህንጻዎች ሲወድሙ፣ 70000 ቤተሰቦች ተጎጅ መሆናቸውን የቬንዙዌላ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር ዶይስዳዶ ካቤሎ ተናግረዋል።












