Afro-Insight News – ፕሬዝደንት ኢሳያሰ አፈወርቂ በግብጽ፥ ካይሮ ለአምስት ቀን ቆይታ ያደረጉት ጉዞ እና ከአቻቸው አል ሲሲ ጋር የሚኖራቸው ውይይት ትኩረት ምን ይሆን በሚል በትኩረት ሲጠበቅ ነበር። የግብጹ ፕሬዝደነት አል ሲሲ የኤርትራን የድንበር ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ግብጽ ያላትን አቋም ዳግም አረጋግጠውላቸዋል።
ኤል ሲሲ የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ትብብር በማስታወስ፥ አሁንም የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን፥ በተለይም ምጣኔ ሃብታዊ እና የመዋዕለ ንዋይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ፍላጎት እንደላቸው ለኢሳያስ ገልጸውላቸዋል።











