Loading...

በታንዛኒያ በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ውጤቱን የተቃወሙ የሟቾች ቁጥር 700 ደርሷል ፣ ፕሬዝደንት ሳሚያ ያለተፎካካሪ አሸንፈዋል።

የምርጫ ኮሚሽኑ ፕሬዝደንት ሳሚያ ምርጫውን  በ98 ፐርሰንት አሸንፈዋል ብሏል። ምርጫው ፍትሃዊ አይደለም የሚሉ ወጣት ሰልፈኞች ፣ መንግስት ዋነኛ ተቃዋሚዎችን ከምርጫው በማገድ ዴሞክራሲዊ ሥርዓትን አፍኗል ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

የታንዛኒያ መንግስት በተቃውሞው የተገደሉት 2 ሰዎች ብቻ ናቸው ሲል ታማኝ የመረጃ ምንጮች የሟቾች ቁጥር 500 እንደሆነ ተናግረዋል።

የአገሪቱ የመከላከያ ሃይሎች ዋና አዛዥ ጃኮብ ምኩንዳ “…የተቃውሞ ሰልፈኞቹ ወንጀለኞች ናቸው፥ ሰልፉም የወንጀል ድርጊት በመሆኑ መቆም አለበት” ብለዋል።

Share this article

ምላሽ ይስጡ

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው